የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ብዙ ፈተናዎችን እያለፈች ከዘመናችን የደረሰች ክርስቶሳዊ ቤታችን ናት። ታሪክ እንደሚመሰክረው በየዘመናቱ የደረሰባት መከራ እና ስደት የራሱን ጠባሳ እየተወ አልፏል። ሆኖም ያለፈው ችግር ለአዲሱ ችግር መሠረት እና መደላድል እየሆነ መከራ እና ስደቱ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየከፋ እና እየባሰ እንዲሄድ አድርጎታል። ከሃምሳ እና ስድሳ ዓመታት ወዲህ በቤተ ክርስቲያናችን ላይ እየደረሰ ያለው ፈተና በዓይነቱም በይዘቱም እጅግ የተለየ እና የከፋ ነው። በተለይ አሁን በሥልጣን ላይ ያለው የሀገሪቱ ገዢ አካል ወደ ሥልጣን ከመጣጀምሮ እየወረደባት ያለው የመከራ ዶፍ በሕልውና ስጋት አፋፍ ላይ እንድንቆም አድርጎናል። ሆኖም በደሙ የመሠረታት ጌታችን እና አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስን ኃይል አድርገን በአንድ ላይ ከቆምን በመድኃኔዓለም ኃይል ከአሸናፊዎች ሁሉ እንበልጣለን። ለዚህም ምሥክሮቻችን በእሳት ወላፈን እና በዉሀ ማዕበል መካከል እያለፉ ሕያው የታሪክ ዓምዶችን ያቆሙልን ጽኑዓን አባቶቻችን እና እናቶቻችን ናቸው። ዛሬ የታሪክ ተረኞቹ እኛ ነን። ይህንን ስጋት ወደ ድል ለመቀየር ተባብረን እንነሣ በሚል መንፈሳዊ ሕሊና የህንን ጉዳይ ጉዳያቸው አድርገው ሊያዩ ለሚችሉ ዓለም አቀፍ እና አሕጉራዊ ተቋማት ድምጻችንን ለማሰማት ትብብራችንን እና አንድነታችንን በፊርማችን እንድንገልጽ ይህ የፊርማ ማሰባሰቢያ ገጽ በሞዓ ተዋሕዶ ተዘጋጅቶ ቀርቧል። ማናችንም ለራሳችን ከፈረምን በኋላ ቢያንስ ሰባት ሰው እንድናስፈርም ስለሃይማኖታቸው ሰማእትነት እየተቀበሉ ባሉት ወገኖቻችን ስም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
ሞዓ ተዋሕዶ
ሰኔ ፲፭ ቀን ፳፻፲፰ ዓመተ ምሕረት
I’m an Ethiopian Orthodox Tewahedo faith believer. It’s sickening to see our Ethiopian Orthodox tewahedo faith followers persecuted, displaced and churches burn.