Skip to main content
Petition for Emergency ECAA Meeting August 24, 2025 2:00 PM

Petition for Emergency ECAA Meeting August 24, 2025 2:00 PM

260 signatures 240 to reach 500
Z
Zeleka W. signed
T
Tsehay G. signed
M
Michael L. signed
W
workneh signed
M
Mulugeta F. signed
A
Abebe K. signed
D
Dana G. signed
S
Sisay G. signed
T
Tesfaye L. signed
T
Temesgen M. signed
DY
Started by Debebe Yirgu 1 year ago

Date of Meeting: Sunday, August 24, 2025

Time: 2:00 PM

Location: 5616 Memorial Drive, Stone Mountain, GA 30083

ይድረስ ለኢትዮጵያ ኮሙኒቲ አባላት በአትላንታ

በመተዳደርያ ደንባችን መሰረት በየሁለት አመት አዲስ የስራ አመራር፣ የቦርድ አባላትና የቁጥጥር ኮሚቴ

በጠቅላላ ጉባኤ እንደሚመረጥ ይታወቃል። በዚህም መሰረት ጁነ . ቀን 2024 አመተ ምህረት በተደረገው

ጠቅላላ ጉባኤ 4 የ ቦርድ አባላት፣ 9 የአመራር ኮሚቴ አባላትና 3 የቁጥጥር ኮሚቴ አባላት መመረጣቸው

ይታወቃል። በተጨማሪም በድርጅታችን መተዳደርያ ደንብ መሰረት የሃይማኖት ተቋማና የተለያዩ

የበጎአድራጎትና የሲቪክ ማህበራት የየድርጅታቸውን የቦርድ አባላት እንዲወክሉ ተደርጓል።

በዚህ መሰረት በጠቅላላ ጉባኤ የተመረጡትና በተለያየ ድርጅቶች የተወከሉት የቦርድ አባላት በድምሩ 22

ነበሩ።

የተከበራችሁ የ ኮሙኒቲ አባላት

እነዚህ ከላይ ከተዘረዘሩት የቦርድ አባላት ጥቂቶቹ ከዳይሬክተሩና ከሌሎች የቦርድ አባላት ጋር በፈጠሩት

አለመግባባትና ውዝግብ ምክንያት የኮሙኒቲው ስራ ተደናቅፏል። የቦርዱ ሊቀ መንበር፣ የቦርድ ምክትል

ሊቀ መንበርና፣ የቦርድ ጸሃፊ በደረሰባቸው ከባድ ዘለፋና አሳፋሪ ዘረኝነት ክሃላፊነታቸው እንዲለቁ

ተገደዋል።

የ2017 የአዲስ ዓመት በአል ከተከበረ በኋል ምንም አይነት ሥራ ለመሥራት ማለመቻሉ ፌብሩዋሪ 2፣

2025 ጠቅላላ ጉባኤ ተጠርቶ ስለችግሩ መግለጫ ካገኘ በኋል መፍትሄ ይሆናል ብሎ ያሰበውን

የሚከተለውን ውሳኔ አሳልፎአል።

1ኛ፣ አዲስ የመተዳደሪያ ደንብ አርቃቂ ኮሚቴ ተመርጦ አወዛጋቢ የሆኑ ጉዳዮችን እንዲመረምርና ተለዋጭ

ረቀቅ ደንብ ለጠቅላላ ጉባኤው አቅርበው እንዲያጸድቁ፣

2፣ የተስተካከለው ደንብ በሚጸድቅበት ቀን አስመራጭ ኮሚቴ እንዲመረጥና አሁን በስራ ላይ ያሉት

አመራሮች ወርደው በአዲስ ተመራጮች እንዲተኩ፣

3፣ ከላይ የተጠቀሱት ሁኔታዎች እስኪሟሉ ድረስ ክአስቸኳይ ሥራዎች ውጪ በማንኛውም የኮሙኒቲው

አካላት ምንም ሥራ እንዳይሠራ ጠቅላላ ጉባኤው ወስኖ ጉባኤው ተበትኗል።

እነዚህ የጠቅላላ ጉባኤው ውሳኔዎች ተግባር ላይ ሳይውሉ፣ በህዝብ የተመረጠውን የአስተዳደር ዲሬክተር

ከስራ አግደው፣ በለውጡ ሌላ ዲሬክተር ሾመው፣ በጆርጅያ መንግሥት ውስጥ ያለውን ምዝገባ ቀይረው፣

የባንክ ሂሳቡን ተቆጣጥረዋል። ይህንን ያደረጉት እኛን አብዛኛውን የቦርድ አባላት አግልለው ጥቂት የቦርድ

አባላት በፈጠሩት የወራሪ ኃይል አማካኝነት መሆኑ እንዲታወቅልን እንጠይቃለን።

ይህ ሁሉ የሀገወጥ ድርጊት አልበቃቸው ብሎ የማህበራችንን ስም በመጠቀም ዲሬክተሩ በአስቸኳይ ከስራ

እንዲወገድ የፍርድ ቤት ክስ መስርተዋል። ይህ ህገወጥ ሂደት ያሳሰባቸው አንድ አንድ ድርጅቶች ለቦርድ

አባልነት የወከሏቸውንና ዲሬክተሩ እንዲነሳ ድምጽ የሰጡት የቦርድ አባላት ድምጻቸው እነሱን የማይውክል

መሆኑን አስታውቀው ውክልናቸውን ማንሳታቸውን በደብዳቤ ለኮሙኒቲው አሳውቀዋል። በዚህም

መሰረት የተስፋ ድርጅትና የማርያም ቤተክርስትያንን ወክልው የመጡት ሁለት ግለሰቦች ከያዙአቸው

የቦርድ አባልነት ተነስተዋል። በተጽኖ ምክንያት ከሃላፊነት የለቀቁትና ከውክልናቸው በድርጅታቸው

የተውገዱት 5 አባላት በመቀነሳቸው በአሁኑ ወቅት የቦርድ አባላት ቁጥር ከ22 ወደ 17 ወርዷል

የተከበራችሁ የኢትዮጵያ ኮሙኒት አባላት በአትላንታ

እኛ ከዚህ በታች ስማችን የተዘረዘረው 10 የቦርድ አባላት በህገወጥ መንገድ መፈንቅለ መንግስት ለማድረግ

በመሯሯጥ ላይ ያሉትን ግለሰቦች ድርጊት አጥብቀን እንቃወማለን። የድርጅታችንን ህልውና ወደአስጊ ደረጃ

አውርደውታል። ሰለዚህም አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ እንዲጠራና ለችግሩ መፍትሄ እንዲሰጠው በጠየቅነው

መሰረት የፊታችን እሁድ August 24, 2025 8:00 pm በኢትዮጵያ ኮሙኒቲ አዳራሽ ስብሰባው እንዲደረግ

ጥሪው በዲረክትሩ በኩል ተላልፏል። ይህ ጠቅላላ ጉባኤ በጣም አስፈላጊ ስለሆነ በድርጅታችን ላይ

እየአንዣበበ የለዉን አደጋ በቅርብ ተገንዝባችሁ ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት በተጠራዉ ጉባኤ ላይ

እንድትገኙ በጥብቅ እናሳስባለን።

የቦርድ አባል

የወከላቸው አካል

1 ደበበ ይርጉ

2 ሶስና በቀለ

3 ታከለ ደበሌ

4 ዲንቃ በቀለ

5 ሳምሶን ሃይለየሱስ

6 አስቴር ሃብተስላሴ

7 የአዛብነሽ ወርቁ

8 ደረጀ መኮንን

9 ጥላሁን መገርሳ

10 ምትኩ ተሾ

We therefore request and support this Emergency Meeting to be held on Sunday, August 24, 2025, at 2:00 PM at the ECAA office, 5616 Memorial Drive, Stone Mountain, GA 30083.


Updates

Reached 250 supporters

August 24, 2025

Reached 100 supporters

August 20, 2025

82 Comments

S
Samson Tegegne
1 year ago Featured

አሁን ግን ነገሮች እየባሱ ስለመጡ ሁሉም አመራሮች ባፋጣኝ እንዲለቁና ለጊዜው ሰላማዊ ለሆነው እድር ተመራጮች አሰረክበው እንዲወጡ እንፈልጋለን። እነዚህ የእድሩ ጠባቂዎች እንደ አስፈላጊነቱ ዶክመንቶችንና አንዳንድ የተጀመሩ ስራዎችን ለማስጨረስ የሚያስፈልጉ ሰዎችን በማቅረብ ለኮሚኒቲው የሚያሳስበውን እያደረጉ አዲሶቹ ተመራጮች እስኪመጡ ኮሚኒቲያችንን ይጠብቁልን።

S
Sisay Abebe
1 year ago Featured

As a community member, I want to know why the elected committee has been unable to effectively serve the community. What is the main obstacle hindering their performance?

T
thewodros abebe
1 year ago Featured

Members from both sides of the aisle should support this emergency meeting. The General Assembly is the only body with the ultimate authority to resolve this ongoing issue, and its action is urgently needed.

S
Saefu A Bishaw
1 year ago Featured

I am aware of some rouge members of the association threat to the ECAA’s very existence to serve the community, therefore, I, Saefu, member of the Community and PR support to have an urgent General assembly to resolve the problem. ECAA must act urgently to resolve the danger it’s facing.

K
Kinfu Damene
1 year ago Featured

I can't help wonder why all this is happening? I wish to understand the main reasons behind the bickering. Does the entity have clearly stated Vision and Mission statements each member, more importantly, those afforded the privilege to serve in various positions understand and can articulate? I very much doubt!

T
Tafesse Belachew
1 year ago Featured

All this entanglement is not for the care of the community. It is “ Let me put my hands on the money” nothing else. where have they been in the past when the community was looking for leadership.

Z
Zeleka Workneh
9 months ago

It’s a must have meeting to save the community at risk at the time.

T
Tsehay Gemeda
10 months ago

Thanks

Help this petition grow

Share it with friends to help reach 500 signatures.

Your share link

Share directly