Skip to main content
ለቅዱስ ሲኖዶስ አንድነት የበኩላችንን እንወጣ

ለቅዱስ ሲኖዶስ አንድነት የበኩላችንን እንወጣ

437 signatures 63 to reach 500
B
Bizu A. signed
W
Weynishet G. signed
G
Girma D. signed
T
Theodros a. signed
D
Diyakon d. signed
S
Someone signed
A
Addisu B. signed
S
Solomon Z. signed
G
Gezahegn T. signed
R
Rabawit signed
GB
Started by Getachew Bekele 8 years, 1 month ago

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ከሁለት አስርት ዓመታት በላይ አስተዳደሯ ለሁለት ተከፍሏል። በዚሁም የተነሳ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት እና ፓትርያሪክ አቡነ መርቆርዮስ በስደት እንደሚኖሩ ይታወቃል።

በቅርቡ በሀገር ውስጥ እና በውጭ የሚኖሩ ብፁዓን አባቶች የተፈጠረውን የሥርዓት መጣስ ለመፍታት እና የቤተ ክርስቲያኒቱን አንድነት ለመመለስ ከሁለቱም በኩል የሚነጋገሩ አባቶች ተመርጠው ለእርቀ ሰላም እየተዘጋጁ መሆኑ ይታወቃል። ለዚህ የተቀደሰ ተግባር የምዕመናን ሁለንተናዊ ድጋፍ ወሳኝ ነው።ለእዚህም ይረዳ ዘንድ ይህ የፊርማ ማሰባሰብያ (ፔቲሽን) ተዘጋጅቷል።

የእዚህ የፊርማ ማሰባሰብ ዓላማ ምዕመናን በአባቶች መለያየት ምክንያት መንፈሳዊ ህይወታቸውን እና ማኅበራዊ አንድነታቸውን በእጅጉ ስለተጎዳ የእርቁን ጉዳይ በጣም ቅድምያ እንደሚሰጡት እና በአንክሮ እንደሚከታተሉት እንዲሁም ከእርቀ ሰላሙ ውጭ ሌላ ምንም አይነት መፍትሄ እንደሌለ ለብፁዓን አባቶች በልጅነት አንደበት ለመማፀን ነው።

ስለሆነም ከእዚህ በታች ያለውን የድጋፍ ፊርማ ማሰባሰቢያ እንዲፈርሙ እንጠይቃለን።

የተሰበሰበው ፊርማ ለሁሉም ብፁዓን አባቶች እንዲታረቁ ከሚጠይቅ የተማፅኖ ደብዳቤ ጋር እርቀ ሰላሙ ከመጀመሩ በፊት ለብፁዓን አባቶች ይላካል።

የእርስዎ በቶሎ መፈረም አስፈላጊ ነውና አሁኑኑ ይፈርሙ::

ለሚያውቁት ኢትዮጵያዊ ሁሉ ይህንን የፊርማ ማሰባሰብያ ሊንክ እንዲልኩላቸው በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን።

ስለትብብርዎ እናመሰግናለን።

Updates

July 8, 2018

We just hit 250 signatures. It is heartening to see this many people united for the peace of our church.

Reached 250 supporters

July 5, 2018

Reached 100 supporters

June 28, 2018

251 Comments

T
Teklai Abera
8 years ago Featured

እግዚኣብሄ ያለ ኣድልዎ ይቅርታን የለገሰው ብዙ ሚስጢር ቢኖረውም፣ ዋናውና ቀዳሚ በሚያስብል፤ ሃጥያት የማይሰራና በእግዚኣብሄር ፊት ኣበሳ የሌለብት የልም። ለዚህም ነው፣ "ከ እፈጣሪ ይቅርታ ባትኖር ኖሮ መንግስተ ሰማያት ባዶ ትቀርነብር" የሚባለው። ኣሁንም እኛም ባዶ እና ያለ ተዋህዳዊ ተስፋ እንዳንቀር ኣባቶች ኣንዲት ተዋህዶ!  ኣንዲት ሲኖዶስ ይወርሱን ዘንድ በእርቀሰላሙ ጥረታቸው እግዚኣብሄር ይርዳቸው

መስታወት ዘውዴ
8 years ago Featured

ክርስቲያን ማለት ይቅር የሚል እና የክርስቶስን ፍቅር በተግባር የሚኖር ነውና እባካችሁ ይቅር ተባባሉና ሀገራችንን እና ሀይማኖታችንን ከጥፋት ታደጉልን እንንታደግ:: እግዚያብሔር ሀገራችንን ኢትዮዺያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!

A
Alemneh Asfaw
8 years ago Featured

ፍቅር ከሁሉም ይበልጣል:: ፍቅር ያሸንፋል:: እያሉ በንባብ ብቻ ሳይሆን በአንድምታ ስለፍቅር ለሚያስተምሩ አባቶች መናገር ድፍረት ባይሆንብኝ በአሁን ወቅት ብቸኛና አማራጭ የሌለው መፍትሔ በፍቅር አንድ መሆን "መደመር" ብቻ ነው:: "እስመ ጻድቅ እግዚአብሔር ወጽድቀ አፍቀረ:: ወርትዕሰ ትሬእዮ ገጾ" "እግዚአብሔር እውነተኛ ነውና እውነትን ይወዳል :; ቅንነት ግን ፊቱን ታየዋለች:: መዝ 10:7

A
Aster Zewdie Bekele
8 years ago Featured

የሰላም አምላክ ቅዱስ እግዚአብሔር ሰላምን ያውርድልን ለቤተክርስቲያናችን አንድነትን ለህዝባችን ሰላምን ይስጠን ለብፁአን አባቶቻችንም አምላክ ልቦና ይስጥልን እርቀሰላሙን ያውርድልን እባካችሁን አባቶች አንድ ሆናችሁ በጎቻችሁን ወደበረቱ አስገቡ!!! አሜን!

E
Ehite Mariam
8 years ago Featured

እባካችሁ አባቶቻችን ከቤተ መንግስት ተማሩ። የእርቅ ተምሳሌት መሆንስ የነበረባችሁ እናንተ ነበራችሁ። ቂም ተቋጥራችሁ ለዘመናት ስትሰው የነበራችሁት መስዋት ጸባኦት እንዴት ይደርሳል? ታረቁ ታረቁ ታረቁ

A
Anonymous
8 years ago Featured

ብፁዓን አባቶቼ! ሰላምን እና ፍቅርን የምትሰብክ ቤተክርስቲያኔ የጥል ምሳሌ ሆና ማየቴ እንዲያበቃ እማጸናችኋለሁ! የምንሰበከው ወንጌል ሐሰት እንዳይመስል! በብፁዓን አባቶች አለመግባባት የደረሰብን ወደር የሌለው ስብራት እና መለያየት፣ መከፋፈል እና ጥላቻ እንዲያበቃ ፍጹም ምኞቴ ነው!

B
Bizu Asmare
7 years ago

E/r selamena fikiren yabzalen ❤Amen.

T
Theodros abrham
8 years ago

Plese be honest

Help this petition grow

Share it with friends to help reach 500 signatures.

Sign Petition

We never post to your account. Social sign-in is used only to verify your signature.

or sign with Email

Add a comment?

Your signature will be added via . Tell others why you're signing — it's optional.

By signing, you accept iPetitions Terms of Service and Privacy Policy.

Share Petition

Don't stop at signing, share the petition link with friends to multiply our impact

Copy link or share directly

Instagram
QR Code