Skip to main content

The news of the reconciliation has finally brought profound peace to our hearts and restored unity to our beloved church. I am overwhelmed with joy knowing that my spiritual home is whole again after so much division. Thank you for walking this difficult path with me and trusting in the …

February 13, 2013

Peace and Unity for Ethiopian Orthodox Tewahedo Church

Peace and Unity for Ethiopian Orthodox Tewahedo Church

🏆 Won — 1,813 supporters Verified

Final supporters

R
roman
ፈቃደ ገ.
S
social b.
S
social b.
G
green m.
D
Demeke T.
S
social b.
B
bookmarks
S
social b.
B
bookmaring s.
+1,803 more
Started by Anonymous 13 years, 9 months ago


በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

“በትሕትና፡ዅሉና፡በየዋህነት፡በትዕግሥትም፤ርስ፡በርሳችኹ፡በፍቅር፡ታገሡ፤

በሰላም፡ማሰሪያ፡የመንፈስን፡አንድነት፡ለመጠበቅ፡ትጉ።” ኤፌ 4:2-3

ለብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ

ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ

ዋሽንግተን ዲሲ

ለብጹዕ አቡነ ናትናኤል

ዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክ ዘኢትዮጵያ እና የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ

አዲስ አበባ: ኢትዮጵያ

ለብጹዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳትና የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት

በያላችሁበት:

ብጹዕ ወቅዱስ አባታችን አቡነ መርቆሬዎስ : ብጹዕ አባታችን አቡነ ናትናኤል እና ብጹዓን አባቶች

ቡራኬያችሁ ይድረሰን !

ጉዳዩ : በቅድስት ቤተክርስቲያናችን ያለውን ልዩነት አስወግዶ ሰላምና አንድነትን ስለማምጣት

እኛ ስማችን ከዚህ በታች የተዘረዘረ በተለያዩ ስፍራዎች የምንኖር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አባላት የሆንን ካህናት፡ ዲያቆናት፡ የሰንበት ት/ቤት አባላት፡ ማኅበራትና በጠቅላላው ማኅበረ ምዕመናን በፓትርያርክ ሲመት ምክንያት ይህች ጥንታዊት፣ ታሪካዊትና ሐዋርያዊት የሆነችው ቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያናችን፤ በሃይማኖትና በሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ሳይሆን በአስተዳደር ከሁለት በላይ መከፈሏ እጅግ ያሳስበናል:: ያሳዝነናልም:: ይኸው መለያየት ሀገሪቱን: ቤተክርስቲያኒቱንና ምዕመናኑን ከባድ ችግር ላይ መጣሉ ይታወቃል:: በቤተ ክርስቲያናችን ላይ የተጋረጡት ዘርፈ ብዙ ችግሮች ሊወገዱ የሚችሉትና መፍትሔ የሚገኝላቸው ፤ ዕርቀ-ሰላም ወርዶ፤ በፍቅር፤ በሕብረት፤ ተቀናጅተን ስንሠራ በመሆኑ አባቶቻችን ከሁሉ በፊት ለሰላምና አንድነታችን ቅድሚያ እንድትሰጡልን፤ ይህን በቤተ ክርስቲያኒቱ ታሪክ ላይ እየተጻፈ ያለውን መጥፎ ታሪክ የሚቀይር ፤ ተስፋ ለቆረጡ ምዕመናንና ምዕመናት የሚያጽናና ታላቅ ገድል እንድትሠሩልን እንለምናለን::

በመጨረሻም አባቶቻችን በሰውና በእግዚአብሔርም ፊት የሚከበሩበትን እርቀ ሰላምና አስተዳደራዊ አንድነትን በማምጣት አንድ ሃይማኖት፣ አንድ መንበር፣ አንድ ፓትርያርክ፣ አንድ ቅዱስ ሲኖዶስ፣ ( ማለትም አንድ እረኛ አንድ መንጋ) እንዲኖረን የሚቻለውን ሁሉ እንድታደርጉ ስለኛ ኃጢአት በመስቀል ላይ ደሙን ባፈሰሰላት በቅድስት ቤተ ክርስቲያን አምላክ እና በእናቱ በወላዲተ አምላክ ስም እንማጸናለን።

የአባቶቻችን አምላክ ቸሩ እግዚአብሔር ለቤተ ክርስቲያናችን ሰላምና አንድነትን፤ ለሀገራችን ዕድገትና ብልጽግናን ያድልልን!

ማሳሰቢያ: የዚህ ፊርማ ማሰባሰቢያ ዓላማው አባቶችን መማጸን ብቻ ነው:: ከገንዘብ ጋራ የተያያዘ ምንም ነገር የለውም::

Updates

December 5, 2012

Seeing one hundred people join this call for reconciliation fills me with such hope for our church. It is deeply moving to know that so many of you share the same heartache over the division of our spiritual home.

Reached 1,000 supporters

December 5, 2012

Reached 100 supporters

December 3, 2012

December 1, 2012

My heart aches to see our holy church divided like this. We are so close to hitting our first milestone and I need you all to send this link to your brothers and sisters in faith today so we can reach these leaders with a united front.

8 Comments

Y
Yonas Davis
13 years ago Featured

Please reconcile. The division is hurting everyone and it needs to end now.

A
Aster Jimenez
13 years ago Featured

በጣም ያሳዝናል! እባካችሁ ተመካክራችሁ ይሄንን ችግር አቁሙት። እግዚአብሔር ይርዳችሁ።

T
Tewodros Ward
13 years ago Featured

አባቶቻችን ሆይ እባካችሁ በቃ በሉን። ቤተክርስቲያናችን አንድ መሆን አለባት። ሰላም እንዲወርድ እንጸልያለን።

D
Dawit Novak
13 years ago Featured

Enough with the politics. Just fix it and bring the church back together. We are tired of this division.

S
Sara Lawson
13 years ago Featured

We need peace. Seeing the church divided like this is heartbreaking for all of us. Please come together for the sake of the faithful.

M
Meklit Palmer
13 years ago Featured

አንድነት የሁላችንም ፍላጎት ነው። እግዚአብሔር አባቶቻችንን አስተዋይ ልቦና ይስጣቸው።

R
roman
8 months ago

Stop killing

ፈቃደ ገብርኤል
3 years ago

ከቤተክርስቲያን በፊት እኔን !